በጋምቤላ ክልል ዲማ ከተማ ከባህል ውጪ በሆነ አለባበስ ምሽት ላይ ዳንስ ቤት የተገኙ ሴቶች የገንዘብ ቅጣት መቀጣታቸውን ተሰማ።
ከማህበረሰቡ ባህል ያፈነገጠ አለባበስ ለብሰው ዳንስ ቤት የተገኙ 13 ሴቶች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በገንዘብ እንዲቀጡ መደረጉን የዲማ ወረዳ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል ::
የዲማ ወረዳ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ኚካሃ አኳይ ለወረዳው መንግስት ኮሙኒኬሽን እንደገለፁት ።
ሴቶቹ ሰሞኑን በዲማ ከተማ ጨለማን ተገን በማድረግ ከባህል ውጪ አለባበስ ለብሰው ከምሽቱ 4:ዐዐ ላይ ዳንስ ቤት በመገኘታቸው ጽ/ቤቱ ከፖሊስ ጋር በመነጋገር በቁጥጥር ስር ውሎው እያንዳንዳቸው 5 ሺህ ብር በአጠቃላይ 65 ሺህ ብር እንዲቀጡ መደረጉን ተናግሯል ::
በመጨረሻም ጽህፈት ቤቱ ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት የጀመረው የቁጥጥር ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ።