በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርርቲያን የኀዘን መግለጫ

Date:

በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርርቲያን ስም እንገልጻለን!!

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ዜና እረፍት የሰማነው በታላቅ ኀዘን ነው። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የሰላም የፍቅር ፣የአንድነት ተምሳሌት አባት ነበሩ።

በአገልግሎት ዘመናቸው ለአገር አንድነትና ለሰላም ቅድሚያ የሚሰጡ፣የርህራሔ እና የፍቅር ሰው በመሆናቸው
በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዘንድ የተወደዱና የተከበሩ የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በመላው ኢትዮጵያን ዘንድ በመልካም ስብእናቸው እና በርሕራሔያቸው በታሪክ ሲታወሱ ይኖራሉ።

በእኒህ የኢትዮጵያውያን ሁሉ አባት በነበሩት በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ዕረፍት የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ታላቅ አረጋዊ ፣ የበሳል አእምሮ ባለቤት፣ አገርን የሚወዱ…

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት...

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስከሬን ሽኝት እየተደረገለት ነው

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስከሬን ከመኖሪያ ቤታቸው...

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የህይወት ታሪክ

ከአባታቸው አቶ ኢድሪስ ዘለቀ እና ከእናታቸው ወ/ሮ መነን ሽፋው፣...