በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርርቲያን ስም እንገልጻለን!!
የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ዜና እረፍት የሰማነው በታላቅ ኀዘን ነው። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የሰላም የፍቅር ፣የአንድነት ተምሳሌት አባት ነበሩ።
በአገልግሎት ዘመናቸው ለአገር አንድነትና ለሰላም ቅድሚያ የሚሰጡ፣የርህራሔ እና የፍቅር ሰው በመሆናቸው
በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዘንድ የተወደዱና የተከበሩ የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በመላው ኢትዮጵያን ዘንድ በመልካም ስብእናቸው እና በርሕራሔያቸው በታሪክ ሲታወሱ ይኖራሉ።
በእኒህ የኢትዮጵያውያን ሁሉ አባት በነበሩት በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ዕረፍት የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።