የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአለም ላይ ያሉ የስደተኞች ቁጥር የሚያሳየዉ “ሁከት የዘመናችን መገበያያ ገንዘብ መሆኑን ነዉ” ብሏል

Date:

የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በአለም ላይ እየጨመረ በመጣዉ በስደተኞች ቁጥር በኩል ወቅታዊ መረጃን በዛሬዉ እለት በሰጠበት ወቅት ነዉ ይህንን ያለዉ፡፡

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ ለፀጥታው ምክር ቤት ሁኔታዉን ሲገልጹ፤”ሁከት የዘመናችን ዋነኛ መገበያያ ገንዘብ ሆኗል” ሲሉ አስረድተዋል፡፡

ግራንዲ በአለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተባብሶ በቀጠለው በየሃገሪቱ ባለዉ ግጭቶች ምክንያት ዜጎች ክፉኛ ችግር ዉስጥ ይገኛሉም ብለዋል።

በተለይ ወደ ሰባት ሚሊዮን የሚጠጉ ስደተኞች ከሱዳንና ዩክሬን የተፈናቀሉ መሆናቸዉንም ኮሚሺነሩ ጠቁመዋል፡፡

ኮሚሺነሩ አክለዉም”በአጭርና በረጅም ጊዜ ደህንነታቸው የተጠበቀና አስተማማኝ ዋስትና እስካልተሰጣቸዉ ድርስ ተፈናቃዮችን ወደ ስፍራቸዉ መመለስ አይቻልም” ብለዋል ሲል የዘገበው የአፍሪካ ኒዉስ ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ...

የትራምፕን ንግግር የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን...

አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፉ የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የአለም አቀፍ የልማት...