የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ቀጥለዋል

Date:

በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 እስከ ምሽት ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደው ነበር።

በዚያው ቀን ምሸት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው የህወሓትና የሰራዊት አዛዦች ቢነጋገሩም ፤ ስለተደረሰው ስምምነት በይፋ ለህዝብ የተሰጠ መረጃ የለም።

ሆኖም ከሰብሰባው አዳራሽ ተቆርጦ የወጣው ቪድዮ እንደሚያመለክተው ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የደመወዝ ፣ የጥቅማጥቅምና ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ የሚውል የመስሪያ ቦታ ጥያቄ አንስተዋል።

የትናንትናው ውይይት ውጤት ለህዝብ ሳይነገር ታድያ ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወደ መቐለ ከተማ የሚያስገባው ዋና አስፋልት ከጥዋት ጀምሮ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ሰዓትና ደቂቃ በሁለት ቦታ ተዘግተዋል።

የትግራይ ኃይል አባላት ሰላማዊ ሰልፈኞች ኣጉላዕና ጉርመዶ በሚባሉ ሁለት ቦታዎች መንገድ በመዝጋታቸው ምክንያት መኪኖች ቆመዋል ተጓዦች ተስተጓጉለዋል።

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ጥያቄያቸው ከትናንትናው ሰልፍ ተመሳሳይ እንደሆነ ቦታው ድረስ ተደውሎ ተረጋግጧል ።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የህዳሴ ግድቡ ውዝግብ በፖለቲካዊ ሳይሆን በቴክኒካዊ መንገድ መፈታት አለበት

በአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ፣ እና የመካከለኛው ምስራቅ...

የ7 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ አለመከናወኑ ተገለጸ

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሚተዳደሩ 7 የጋራ መኖሪያ...

የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ በ80 ዓመታቸው ከዚህ...