የአምባሳደር መለስ መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል

Date:

አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ”የኢትዮጵያ እናየ ኬንያ ስጋት እና ተስፋ” በሚል ርዕስ ያዘጋጁት አዲስ መጸሐፍ  በነሐሴ ወር መጨረሻ  ላይ ለንባብ እንደሚበቃ ተገለጸ፡፡

አገራቸውን በዲፕሎማሲው መስክ  ከሀያ ዓመታት  በላይ ያገለገሉት አምባሳደር መለስ ዓለም፤ በጋዜጠኝነት ሙያ መሥራታቸውም ይታወቃል፡፡

የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ያገኙ ሲሆን፤ በትምህርቱ ዓለም የገፉበት መስክ ደግሞ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ነው።

የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ደግሞ ከስዊዘርላንድ የማኔጅመነት ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ግንኙነት አግኝተዋል።

አምባሳደሩ በኬንያ ማላዊና ሲሸልሰ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው አገራቸውን አገልግለዋል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል፣ በጎረቤት አገራት ዳይሬክተር ጄኔራልነትና በቃል አቀባይነት ያገለገሉም  ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል ሆነው እየሠሩ ነው።

አምባሳደር መለስ ዓለም  ከአሁን በፊት በምሥራቅ አፍሪካ ላይ አተኩረው በሚሰሩ ጋዜጦች ላይ የአገራቸውን ጥቅም ያስቀደሙና ቀጣናዊ ትስስርን የሚያበረታቱ ጽሑፎችን አሳትመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ...

የትራምፕን ንግግር የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን...

አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፉ የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የአለም አቀፍ የልማት...