ሽልማቱ ለሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ማስታወሻ ይሁንልኝ

Date:

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ሽልማትን ለሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር መታወሻነት እንዲሆንለት ሰይፉ ፋንታሁን ጠይቋል፡፡

በሚዲያው ዘርፍ የዘንድሮ የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚ የሆነው ታዋቂው የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያው ሰይፉ ፋንታሁን ይህ ሽልማት ሜቄዶንያን ለማስታወስ ሊሆን እንደሚገባ አስታውቋል፡፡

በዘንድሮ የ2025 የአፍሪካ ኢምፓካት አዋርድ የአየር መንገዱ አቶ መስፍን ጣሰው፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ ድምፃዊ መሃሙድ አህመድ፣ ጆ ማሞ እና ሰይፉ ፋንታሁንን ተሸላሚ አድርጓል፡፡

ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የሚሰናዳ ነው።

በየአመቱ ከስፖርት፣ ከስነ ጥበብና ከስራ ፈጠራ ዘርፎች ለማህበረሰቦቻቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦና ለለውጥ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ከየዘርፉ ተመርጠው የሚሸለሙበትም መድረክ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

‹‹ኢሳያስ አፈወርቂ ከአገር ይኮበልላሉ››

የቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ሻብያን ነክሰው ይዘዋል፡፡ ዛሬ ደግሞ፣ ፕሬዝዳንት...

የቀድሞው የዶናልድ ትራምፕ አማካሪ ጆን ቦልተን ተከሰሱ

ጆን ቦልተን በሪፐብሊካኑ የመጀመሪያው ዙር የፕሬዚዳንትነት ወቅት የብሄራዊ ደህንነት...

“ወደራስ መመለስ!”

በ99ኛ የስብሐቲዝም መድረክ ከፍልስፍና መምህሩና ጋዜጠኛ ደረጀ ይመር ጋር...