በአዲስ አበባ ለጨረታ ለቀረቡ ቦታዎች በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሰጠቱ ታወቀ

Date:


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ ለጨረታ ካቀረባቸው 427 ቦታዎች ውስጥ፣ የቀረበው ከፍተኛ ዋጋ በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሆኑና ቦታውም ካዛንቺ እንደሆነ ታወቀ፡፡፡
የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት ባንክና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በአምስተኛ ዙር እየተካሄደ በሚገኘው የመሬት ሊዝ ጨረታ 18 ሔክታር መሬት ቀርቧል፡፡
በሊዝ ለማጫረት ከቀረቡ ቦታዎች ውስጥ ካዛንቺስ የሚገኝ አንድ ቦታን በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር ለመግዛት ከተጫራች ዋጋ መቅረቡን፣ እስካሁን በአምስት ክፍላተ ከተሞች በተደረገው የጨረታ ሒደት 76 ተጫራቾች በጊዜያዊነት ጨረታውን ማሸነፍ መቻላቸውን አክለው ገልጸዋል፡፡
ለጨረታው የቀረቡ ቦታዎች የሚገኙት በዘጠኝ ክፍላተ ከተሞች እንደሆኑ የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ በአጠቃላይ የጨረታ ሰነዱን ገዝተው የተጫረቱት ብዛት 6,885 ተጫራቾች  እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
@ሪፖርተር

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...