ሕብረት ባንክ ከአፍሬክሲም ባንክ የ50 ሚሊዮን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ዋስትና አገኘ

Date:

ሕብረት ባንክ ከአፍሪካ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ (አፍሬክሲም ባንክ) ጋር ያለውን ስምምነት በማደስ የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ዋስትና ማግኘቱን አስታወቀ።

የተገኘው የዋስትና ስምምነት በአፍሬክሲም ባንክ የትሬድ ፋሲሊቴሽን (AFTRAF) ፕሮግራም ስር የሚፈጸም ሲሆን፣ ሕብረት ባንክ ለሚከፍታቸው የሌተር ኦፍ ክሬዲት እና በወጪና ገቢ ንግድ ላይ ለተመሠረቱ የፋይናንስ ሰነዶች ዋስትና የመስጠት አቅም ይሰጠዋል።

በዚህ ስምምነት አማካይነት ሕብረት ባንክ ከዓለም አቀፍ ባንኮች ጋር በበለጠ ቅልጥፍና ለመስራት እንደሚያስችልም ተገልጿል።

በደንበኞችና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ዘንድ ያለውን ተዓማኒነት እንደሚያጎለብተው ባንኩ ገልጿል። በተጨማሪም ይህ ስምምነት የባንኩን የንግድ ፋይናንስ አቅም በእጅጉ የሚያሳድግ እንደሆነ ታውቋል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ለሊት እንቅልፍ የለኝም

"አሁን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ ያሳስበኛል፤ እኔ አሁን 86 ዓመት...

አዎ ነበሩ ….

🔘የሁሉም አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሓጅ ዑመር🔘ነፍስዎ በሰላም ትረፍ "...

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ሳር ቅጠሉ የሚወዳቸው

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ሳር ቅጠሉ የሚወዳቸው የሀይማኖት...