“ሕወሓት ‘የምመራው ሠራዊት አለኝ’ ማለቱ ተቀባይነት የለውም”

Date:

የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የሕወሓት ሠራዊት የሚባል ነገር እንደሌለና ሕወሓትም ሠራዊት ሊኖረው እንደማይችል ትላንት ምሽት ለኢዜአ በሠጡት ቃለ ምልልስ ላይ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው፣ ሕወሓት ‘የምመራው ሠራዊት አለኝ’ ማለቱ ተቀባይነት እንደሌለውም ገልጸዋል።

ሕወሓት ለ50 ዓመታት ባንድ ቦታ ላይ ተቸንክሮ የቀረና በሌሎች መስዋዕትነት ኅልውናውን ለማስቀጠል የሚፈልግ ድርጅት ነው ሲሉ የተቹት አቶ ጌታቸው፤”የዚህ ድርጅት አባል ሆኖ መቀጠል በራሱ አስቀያሚ ነገር ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

በትላንትናው ምሽት ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የፌደራል መንግሥቱን ወክለው የፕሪቶሪያውን ስምምነት የተደራደሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንም ከኢዜአ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ቃል አቀባይዋ ዩክሬን የአፍሪካ ሀገራትን መበቀል ትፈልጋለች አሉ

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ኪዬቭ የአፍሪካ አገራት...

ሕጻኑ በሀገሪቱ የመጀመሪያ በሆነ ቀዶ ሕክምና ተወለደ

የ28 ዓመቷ ወይዘሮ ሰናይት ታምራት ቀደም ሲል በነበረው እርግዝናዋ...

ግብፅ የኤርትራን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንዲከበር ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች

የግብፅ ፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አልሲሲ፤ የኤርትራን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት...