በአሜሪካ ሳን ዲያጎ አካባቢ በተከሰከሰ አውሮፕላን ምክንያት በርካታ ቤቶች እና መኪናዎች በእሳት ተያይዘዋል፡፡
የአደጋው መንስኤ ምን እንደሆነ እና የደረሰው ጉዳት መጠን ምን እንደሆነ እስካሁን አለመታወቁን ሲኤንኤን ዘግቧል።
አደጋ የደረሰባት አውሮፕላን ከስድስት እስከ ስምንት ሰዎችን ማጓጓዝ የምትችል ሴስና 550 የምትባል ሲሆን፣ በአደጋው ወቅት በአካባቢው ደመናማ የአየር ሁኔታ እንደነበር ታውቋል።
