በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ዕጣ ፈንታቸው ወደ ኤሌክትሪክ መቀየር ነው

Date:

በነዳጅ የሚሠሩና አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ተሽከርካሪዎች ዕጣ ፈንታቸው ወደ ኤሌክትሪክ መቀየር ነው ሲል የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ለመቀየር ስታንዳርድ ፀድቆ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።

ኃላፊው፤ የኤሌክትሪክ መኪና በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ ባለበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያም ከ100 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን ወደ ገበያው ማስገባት ችላለች ማለታቸውን ኢፕድ ዘግቧል።

በመጪዎቹ 10 ዓመታት ወደ ሀገር ውስጥ ከሚገቡ ተሽከርካሪዎች መካከል “95 በመቶ የሚሆኑትን የኤሌክትሪክ ለማድረግ” እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት የኤሌክትሪክ መኪና ምርትን ለማፋጠን፣ የነዳጅ ወጪን ለመቀነስ እና አረንጓዴ ከባቢን ለመገንባት አቅዶ እየሠራ ሲሆን፤ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥም ከ500 ሺህ በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የማሌዥያ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲ ከ43 ዓመታት በኋላ ተከፈተ

ማሌዥያ በአዲስ አበባ የነበራትን ኤምባሲ ከ43 ዓመታት በኋላ ዳግም...

ህጻናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ ተመረቀ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚሰሩ የልማት ሥራዎች ሁሉ ኪነ...

ትራምፕ ውሸታም ናቸው- የኮንግረስ አባል ኢልሀን

የኮንግረስ አባል ኢልሀን ኡመርና የፕሬዝደንት ትራምፕ ውዝግብ እንደቀጠለ ነው፡፡...

የአውሮፓ ህብረት አመነ

የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የኮቪድ ክትባት ትክክለኛ የጤና ቁጥጥር ሂደቶችን...