ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ለመተግበር ደንብ አወጣች

Date:

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነትን በይፋ ለመተግበር የሚያስችል ደንብ ማውጣቷን አስታውቃለች።

በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው ደንብ ቁጥር 574/2017፣ ከአባል ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ በሚገቡ ዕቃዎች ላይ የሚደረገውን የጉምሩክ ቀረጥ ቅነሳ በዝርዝር አስቀምጧል።

በነጋሪት ጋዜጣ በታተመዉ ደንብ መሰረት፣ ዕቃዎች በሶስት ምድቦች የተከፈሉ ሲሆን፣ ከ90% በላይ የሚሆኑት ዕቃዎች በ10 ዓመታት ውስጥ ቀስ በቀስ እየቀነሱ በመሄድ ሙሉ በሙሉ ከቀረጥ ነፃ ይሆናሉ። ሌላኛው የምድብ “ለ” ዕቃዎች ከ7% አይበልጡም፣ እነሱም ከ2026 ጀምሮ በ8 ዓመታት ውስጥ ከቀረጥ ነፃ ይሆናሉ።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ታሪፍ ሰንጠረዥ ተፈጻሚ የሚሆንባቸውን አባል ሀገራት የሚገልጽ ሲሆን፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ደግሞ የዕቃዎችን ምድብ የመለየት እና የማስተካከል ስልጣን ተሰጥቶታል። በተጨማሪም፣ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ለዕቃዎች የሥሪት ሀገር የምስክር ወረቀት ይሰጣል።

ይህ ደንብ ከነሐሴ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ይበልጥ እንዲቀላቀል እና አዲስ የንግድ እድሎችን እንዲፈጥር ይጠበቃል ሲል ካፒታል አስነብቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና የወሰዳችሁ

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት...

የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰራዊት አባላት ተጠቃሚ የሚያረጋግጥ ደንብ ማጸደቁ አስታውቋል

እሁድ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመረው የትግራይ ኃይል ሰልፍና ተቃውሞ...

የኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ

በ80 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የኬንያ የቀድሞ...