ዳይመንድ ሊግ በጉዳፍ ፀጋይ አሸናፊነት ተጠናቋል

Date:


የዋንዳ ዳይመንድ ሊግ ከአንድ ወር ያላነሰ የእረፍት ጊዜ በኋላ ዛሬ ቅዳሜ ወደ ውድድር ሲመለስ ኢትዮጵያዊቷን ጀግና አትሌት ጉዳፍ ፀጋይን በአሸናፊነት አንግሷል።

የአለም አይኖች ሁሉ ያረፉበት የፖላንዷ ሲሌሲያ የ1500 ሜትር ዳይመንድ ሊግ፣ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ 3:50:73 በመግባት አሸናፈነቷን አውጃለች፡፡

ከውድድሩ በፊት ለማሸነፍ ብቻ ሳይሆን ለሪከርድም ነው የምሮጠው ያለችው ኬንያዊቷ አትሌት ባትረስ ቼቤት ከጉዳፍ አራት ሰከንድ አካባቢ ዘግይታ በመግባት በሁለተኛነት፣ ጆርጂያና ሀንተር ቤል ደግሞ በሦስተኛነት አጠናቀዋል፡፡

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ የገባችበት 3:50:73 የሲዝኑ ምርጥ ሰዓቷም ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

  1. ጉዳፍ ፀጋይ 3:50.62 MR, SB
  2. ቤትሪስ ቼቤት 3:54.73 PB
  3. ጂኦርጂያ ሀንተር ቤል 3:56.00
  4. በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና የወሰዳችሁ

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት...

የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰራዊት አባላት ተጠቃሚ የሚያረጋግጥ ደንብ ማጸደቁ አስታውቋል

እሁድ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመረው የትግራይ ኃይል ሰልፍና ተቃውሞ...

የኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ

በ80 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የኬንያ የቀድሞ...