በአማራ ክልል በርካታ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች ግብራቸውን አላሳወቁም

Date:

​አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ውስጥ ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ቢሰበስብም፣ አብዛኛዎቹ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ባለማሳወቃቸው በቀሪ ጊዜያት እንዲከፍሉ አስጠነቀቀ።

​የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር ትምህርት እና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታዘባቸው ጣሴ ፤ ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት 100.3 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ እስከ መስከረም 27/2018 ዓ.ም በተሰበሰበው ዕለታዊ መረጃ መሠረት ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል።

​ይህ አፈጻጸም ቢኖርም፣ በክልሉ ካሉ 22,930 የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች መካከል በዚህ ሦስት ወር ውስጥ ግብራቸውን አሳውቀው የከፈሉት 4,004 ብቻ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

አቶ ታዘባቸው በርካታ ግብር ከፋዮች አሁንም
ግብራቸውን አሳውቀው እንዳልከፈሉ በመግለጽ፣ በቀሪ ጊዜያት ግብራቸውን አሳውቀው እንዲከፍሉ ጥሪ ማቅረባቸውን አሚኮ ዘግቧል።

የገንዘብ ሚኒስትር ከዚህ ቀደም በአዲሱ በገቢ ግብር (ማሻሻያ) አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ላይ ማብራሪያ እንደሰጠዉ፤  በየሶስት ወሩ የሚከፈለው ግብር ተፈጻሚ የሚሆነው ግብር ከፋዩ የሂሳብ ሪፖርት ከሚያቀርብበት ወር መጨረሻ ጀምሮ ካለው የሶስት ወር ጊዜ በኋላ በሚኖረው የ30 ቀን ጊዜ ውስጥ ነዉ ማለቱ ይታወሳል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ከዓለም የፕሬስ ነጻነት ጀግና ሽልማት ተሸላሚዎች አንዱ ሆኖ ተመረጠ 

ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” መስራቾች አንዱ የሆነው ተስፋለም ወልደየስ፤ ዓለም አቀፉ...

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ) እየተዘጋጀ ነው

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘ ዓለምአቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ)...

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ወደ ውጪ ሃገር ለሚላኩ ጭነቶች የስሪት አገር ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰጠ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ስምምነት መሠረት...

የ3D ኮንክሪት ፕሪንት ቴክኖሎጂ አቅራቢው ባውሚት ኦስትሪያ ኢትዮጵያ ገባ

በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና ባውሚት ኦስትሪያ መካከል በነበረው የመግባቢያ...