ኤርትራ የኢትዮጵያን ክስ “ወታደራዊ ጠብ አጫሪነት” ነው አለች

Date:

ኢትዮጵያ ጦርነት ልትከፍትብኝ እየተዘጋጀት ነው ስትል የከሰሰቻት ኤርትራ፤ ክሱን “ወታደራዊ ጠብ አጫሪነት” ስትል ውድቅ አደረገች።

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል፤ «የቀድሞ ግዛትን ለማስመለስ ያለመ” ያሉትን ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ፣ ወታደራዊ የጠብ አጫሪነት የታከለበት ነው ሲሉ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉተሬቭ በላከው ደብዳቤ አስመራ ፣ ፅንፈኛ ካለው የህወሓት አንጃ ጋር ኢትዮጵያን ለመውጋት እየተዘጋጁ ነው ሲል ከሷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞትዮስ የፈረሙበት ይህ ደብዳቤ፤ የፌደራል መንግሥት ወታደሮች ከአማጽያን ጋር በሚዋጉበት በአማራ ክልል «ሁለቱ አካላት የታጠቁ ቡድኖችን ይደግፋሉ፣ ያንቀሳቅሳሉ ይመራሉም” ሲልም ይወቅሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...