ኤርትራ የኢትዮጵያን ክስ “ወታደራዊ ጠብ አጫሪነት” ነው አለች

Date:

ኢትዮጵያ ጦርነት ልትከፍትብኝ እየተዘጋጀት ነው ስትል የከሰሰቻት ኤርትራ፤ ክሱን “ወታደራዊ ጠብ አጫሪነት” ስትል ውድቅ አደረገች።

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል፤ «የቀድሞ ግዛትን ለማስመለስ ያለመ” ያሉትን ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ፣ ወታደራዊ የጠብ አጫሪነት የታከለበት ነው ሲሉ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉተሬቭ በላከው ደብዳቤ አስመራ ፣ ፅንፈኛ ካለው የህወሓት አንጃ ጋር ኢትዮጵያን ለመውጋት እየተዘጋጁ ነው ሲል ከሷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞትዮስ የፈረሙበት ይህ ደብዳቤ፤ የፌደራል መንግሥት ወታደሮች ከአማጽያን ጋር በሚዋጉበት በአማራ ክልል «ሁለቱ አካላት የታጠቁ ቡድኖችን ይደግፋሉ፣ ያንቀሳቅሳሉ ይመራሉም” ሲልም ይወቅሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...