በመዲናዋ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ ርምጃ ይወሰዳል

Date:

በአዲስ አበባ በመሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ላይ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት ቁጥጥር እየተደረገ ነው አለ የከተማዋ ንግድ ቢሮ፡፡

በቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ ብርሃኑ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ በመዲናዋ ያለውን የመሰረታዊ ፍጆታ እቃዎች አቅርቦት ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

በዚህ መሰረትም በከተማዋ በሚገኙ ትላልቅ የገበያ ማዕከላት የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች በስፋት ለተጠቃሚዎች እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በሁሉም ወረዳዎች በሚገኙ 219 የእሑድ ገበያዎች መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት፡፡

የግብርና እና የኢንዱስትሪ ውጤቶች በእሑድ ገበያዎች በስፋት እንዲቀርቡ የገበያ ትስስር መፈጠሩንም አመልክተዋል፡፡

በሌላ በኩል ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች አስፈላጊው ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡

ምርት በሚደብቁና በሚያከማቹ ስግብግብ ነጋዴዎች ላይ ልዩ ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል፡፡

የቁጥጥር ሥራው እስከታችኛው መዋቅር መዘረጋቱን ጠቁመው ÷ ሕብረተሰብ ሕገ ወጥ ነጋዴዎች ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡

አላስፈላጊ ዋጋ በመጨመር ብሎም ምርት በማከማቸት የገበያ አለመረጋጋትን ለመፍጠር በሚያሴሩ ነጋዴዎች ላይ የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ ይወሰዳል ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

(ኤፍ ኤም ሲ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በአማራ ክልል በርካታ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች ግብራቸውን አላሳወቁም

​አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት...

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ) እየተዘጋጀ ነው

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘ ዓለምአቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ)...

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ወደ ውጪ ሃገር ለሚላኩ ጭነቶች የስሪት አገር ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰጠ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ስምምነት መሠረት...

የ3D ኮንክሪት ፕሪንት ቴክኖሎጂ አቅራቢው ባውሚት ኦስትሪያ ኢትዮጵያ ገባ

በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና ባውሚት ኦስትሪያ መካከል በነበረው የመግባቢያ...