የሁላችንም አባት የነበሩት የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ወደ አኼራ ሄደዋል::
የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ አኼራ ሄደዋል::
ህልፈታቸው የመላው ሀገራችን ህዝብ ሀዘን ነው:: እኚህን ታላቅ አባት ላበርክቷቸው በሚመጥን መልኩ ስርዓተ ቀብራቸው በመንግስት ደረጃ ኢስላማዊ ስነ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ መፈፀም ይኖርበታል::
ሀገራችን ታላቅ አባት አጥታለች:: ሀዘናችን መሪር ቢሆንም የአላህን ውሳኔ ከመቀበል ውጪ አማራጭ የለም::
አላህ መልካም አበርክቷቸውን ይቀበላቸው፣ ምህረቱን ይለግሳቸው፣ በጀነተል ፊርዶስ ይመንዳቸው
ከኡስታዝ አቡበከር አህመድ