ግለሰቦቸ እና ተቋማት ራሳቸውን ከሳይበር ጥቃት እንዲከላከሉ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) አሳስቧል፡፡
በአስተዳደሩ የተቀናጀ የሳይበር መከላከል አገልግሎት ዲቪዥን ሃላፊ አቶ አቤል ተመስገን እንዳሉት÷ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እየተስፋፋ መሆኑን ተከትሎ የሳይበር ጥቃቶች ውስብስብ እየሆኑ መጥተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የሳይበር ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደሚገኝ ጠቅሰው÷ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 7 ሺህ 514 የጥቃት ሙከራዎች መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
እነዚህ ጥቃቶች አብዛኞዎቹ በግለሰብ እና ተቋማት ላይ የተሞከሩ መሆናቸውን ያስረዱት ሃላፊው ÷ ግለሰቦቸ እና ተቋማት ራሳቸውን ከሳይበር ጥቃት መከላከል የሚያስችል ግንዛቤ እና አቅም ሊኖራቸው እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በተለይም ግለሰቦች በቴሌግራም የሚላኩ ያልታወቁ ሊንኮችን ባለመክፈት፣ የይለፍ ቃላቸውን በማዘመን እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚተላለፉ ሀሰተኛ ምስሎችንና መረጃዎችን በመለየት ራሳቸውን ከጥቃት መከላከል እንደሚችሉ አብራርተዋል፡፡
FMC
ግለሰቦቸና ተቋማት ራሳቸውን ከሳይበር ጥቃት ይከላከሉ
Date: