በቋንቋ፣ በባህልና በማኅበረሰብ ልማት ዘርፎች ያበረከቷቸው የሕይወት ዘመን አገልግሎቶች “አጋዝ” የሚል ባህላዊ ስያሜ አሰጥቷቸዋል፥ አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም።
አጋዝ ገብረየሱስ በጉራግኛ፣ አማርኛ እና እንግሊዝኛ 16 መጽሐፍትን ጽፈዋል። ለጉራጌ ባህልና ቋንቋ ልማት ካበረከቱት አስተዋጽኦ ባሻገር የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን (ገህራልድ) መሥርተዋል፣ አገልግለዋልም። በሌሎች ሀገራዊና ዓለምአቀፍ ተቋማትም አሻራቸውን አኑረዋል።
በበርካታ ስራዎቻቸው የሚታወቁት እኚህ ታላቅ ሰው ሌላም ያልተለመደ ድንቅ ተግባር ፈፅመዋል።
ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ጋር በመተባበር ይህንኑ ስራቸውን ”ድንቁ ቅፅበት” ብሎታል። ድንቁ ቅፅበት ምንድነው? ቅዳሜ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ከረፋዱ 4:00 ጀምሮ በወመዘክር ኅሩይ አዳራሽ ታላላቅ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በደማቅ መርሐ-ግብር ይፋ ይደረጋል።
በእለቱ የደራሲው ተወዳጅ መጻሕፍትና ሌሎች ታሪካዊ ስራዎች ይሰነዳሉ፤ ለትውልድም ይበረከታሉ።
‘
