ዋሺንግተን ንግግር እየተደረገ መሆኑን ስትገልጽ ቴህራን በበኩሏ ወዲያውኑ ውድቅ አድርጋለቸ። ይህ አለመግባባት የሚያሳየው ሁለቱ አገራት ከዚህ በፊት ባደረጓቸው ድርድሮች ወቅት የተፈጠረን ጥልቅ አለመተማማን ነው።
ከዚህ ቀደም በሁለቱ አገራት መካከል ሁለት ጊዜ ውጥረትን ያረግባሉ የተባሉ ንግግሮች ተጀምረው ነበር።
ነገር ግን ሁለቱም ንግግሮቹ በሂደት ላይ እያሉ አሜሪካ እና እስራኤል በቴህራን ላይ ወታደራዊ ጥቃት ከፍተውባታል።
ከኢራን አንጻረ ንግግር መጀመር ጦርነት ይከፈታል የሚለውን ዕድል አይቀንሰውም።
እንዲያውም ጦርነቶቹ የተጀመሩት ንግግሮቹ እየተካሄዱ ባለበት ወቅት ነው። ለዚህም ነው የትራምፕ ንግግር በጥርጣሬ የታየው።
ነገር ግን የኢራን ማስታባበያም ቢሆን እውነታውን አያሳይም። ከመጋረጃ ጀርባ በርካታ ነገሮች የተከናወኑ ነው።
ዲፕሎማሲን የሚደግፉ ባለሥልጣናት ሳይቀር ጫና ውስጥ ናቸው። በድጋሚ ድርድር መጀመር አደገኛ ሊሆን ይችላል።
አሁን የሚደረግ ድርደር ከዚህ ቀደም ከተካሄዱት የተለየ የሚሆንበትን መንገድ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም። ለዚህም ነው የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባሰ አራጋቺን ጨምሮ ሊሎች የአገሪቱ ባለሥልጣናት ጠንካራ ድምጸት ባለው ቃል ንግግርን ውድቅ የሚያደርጉት።
