አዲስ የወጣ ዓለም አቀፍ ሪፖርት እንዳመለከተው፣ ኬንያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀም ከዓለም አንደኛ ሆናለች። በሪፖርቱ መሠረት፣ በሀገሪቱ ካሉ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ውስጥ 97.5 በመቶ የሚሆኑት ባለፉት አንድ ወር ውስጥ ቢያንስ አንድ የAI ቴክኖሎጂ ተጠቅመዋል።
ይህ ቁጥር ከተጠኑት 54 ሀገራት ሁሉ ከፍተኛው በመሆኑ ኬንያን ቀዳሚ አድርጓታል፤ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በ94.2 በመቶ ሁለተኛ፣ ኢንዶኔዥያ ደግሞ በ93.6 በመቶ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ይህ ከፍተኛ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ከሀገሪቱ የAI ዘርፍን በሕግ የማዋቀር ጥረት ጋር የተያያዘ ነው። በአንፃሩ እንደ አሜሪካ (71.5 በመቶ) እና ዩናይትድ ኪንግደም (62.8 በመቶ) ያሉ ታላላቅ ምዕራባውያን ሀገራት ከዚህ ውጤት በታች ይገኛሉ።
በዓለም አቀፍ ደረጃ በወር ውስጥ የAI ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ ሰዎች ቁጥር 4.02 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ ሰዎች AIን የሚጠቀሙት መረጃዎችን ለመፈለግ ነው።
capital fm kenya-
