“የሶማሊያ አሸባሪዎችን ለጠቆመኝ 10 ሚሊዮን ዶላር እከፍላለሁ” አሜሪካ

Date:

አሜሪካ በሶማሊያ የሚገኘውን የአይ ኤስ አይ ኤስ የፋይናንስ ኦፕሬሽን ክንፍ በተመለከተ መረጃ ለሚሰጥ ሰው የ10 ሚሊየን ዶላር ሽልማት እንደምትጥ አስታወቀች።

የአሸባሪው አይ ኤስ አይ ኤስ በአፍሪካ ዋነኛ መቀመጫ ናት በተባለችው ሶማሊያ የሚገኘው የፋይናንስ ክንፍን አስመልክቶ መረጃን ለሚሰጣት ግለሰብም ሆነ ተቋም ሽልማት እንደምትሰጥ ነው አሜሪካ ያስታወቀችው።

የፋይናንስ መረጃዎችን የሚሰጡ ሰዎች ከገንዘብ ሽልማቱ በተጨማሪ ደህንነቱ ወደተጠበቀ ቦታ እንደሚዘዋወሩም ተገልጿል።

አሜሪካ ቡድኑ በማጭበርበር ፣ በመዝረፍ እንደዚሁም ሰዎችን በማገት ገንዘብ ይሰበስባል ያለች ሲሆን በተጨማሪ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና ህገ ወጥ የአሳ ማስገር ተግባራት ትርፍ እያገኘ ነው ብላለች።

አይ ኤስ አይ ኤስ ሶማሊያ በ2015 በአብዱልቃድር ሙሚን አመራር ስር የተመሰረተ ሲሆን ይኸው ግለሰብ በ2025 ወደ አይ ኤስ አይ ኤስ አለም አቀፍ አመራርነት አድጓል ተብሏል።

አሜሪካ በቅርቡ በሶማሊያ ያለው አል ካራር የተባለ ቢሮ የቡድኑ የፋይናንስ ማዕከል ሆኖ እየሰራ መሆኑን መግለጿ ሲታወስ በክሪፕቶከረንሲ መልክ ገንዘቡ እንደሚዘዋወርም ገልፃ ነበር።

አይ ኤስ አይ ኤስ ለአፍሪካ ቀንድ አሁንም ስጋት ሲሆን በቅርቡ ኢትዮጵያ በፑንትላንድ ሰልጥነዋል የተባሉ 82 አባላቱን መያዟ መዘገቡ ይታወሳል ሲል ሀገሬ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በአማራ ክልል በርካታ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች ግብራቸውን አላሳወቁም

​አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት...

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ) እየተዘጋጀ ነው

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘ ዓለምአቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ)...

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ወደ ውጪ ሃገር ለሚላኩ ጭነቶች የስሪት አገር ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰጠ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ስምምነት መሠረት...

የ3D ኮንክሪት ፕሪንት ቴክኖሎጂ አቅራቢው ባውሚት ኦስትሪያ ኢትዮጵያ ገባ

በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና ባውሚት ኦስትሪያ መካከል በነበረው የመግባቢያ...