ታላቁ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብን በመቀልበስ የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ቁልፍ የትብብር መሠረት መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
በሁለተኛው የኢትዮጵያ ውሃና ኢነርጂ ሳምንት መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፤ ሀገሪቱ በውሃና ኢነርጂ ልማት ዘርፍ የምታከናውናቸው ተግባራት በድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ላይ አስተማማኝ የውሃ ፍሰት በመፍጠር ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንዳደረገ አንስተዋል።
የኢትዮጵያ የውሃ፣ የነፋስና የጸሐይ የኃይል አቅርቦት ልማት የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመቀነስ በቀጣናው አስተማማኝ የሆነ የታዳሽ ኃይል አቅርቦትን እየፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከጥቅምት 17 – 21 ባሉት ቀናት በሚካሄደው 2ኛው የኢትዮጵያ ውሃና ኢነርጂ ሳምንት፤ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የግንባታ ሂደት ወቅት ኢትዮጵያ ከተፋሰሱ ሀገራት ጋር ባከናወነችው የትብብር ተግባራት ዙሪያ የማስገንዘብ ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።
