“ሩሲያውያን አውሮፓን ይወራሉ” የሚሉ ንግግሮች ከእውነት የራቁ ናቸው ሲሉ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ለጋዜጠኛ ታከር ካርልሰን ተናግረዋል።
ዊትኮፍ ያነሷቸው ሌሎች ዋና ዋና ነጥቦች፡-
🟠 የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካ አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥሉት ወራት ሊገናኙ ይችላሉ።
🟠 የዋሽንግተን እና ሞስኮ ድርድር ከፍተኛ መሻሻል ተገኝቶበታል።
🟠 በሚቀጥለው ሳምንት በጥቁር ባህር ላይ ጥቃት እንዲቆም የሚያስችል ስምምነት ሊደረግ ይችላል።
🟠 ኪዬቭ በዩክሬን ምርጫ ለማካሄድ ተስማምታለች።
🟠 ዘለንስኪ እና የአስተዳደራቸው የበላይ ዩክሬን የኔቶ አባል እንደማትሆን በአብዛኛው ተስማምተዋል።
🟠 ከሩሲያ ጋር የሰላም ስምምነት ከተደረሰ ኪዬቭ የሕብረቱ አባል አትሆንም።
🟠 ግጭቱን ወደ ኒውክሌር መካረር ውስጥ ይከታል ብላ ስለምታምን፤ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የሚደረገውን የገንዘብ ድጋፍ መቀጠል አትፈልግም።
