በፍሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የ60 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ተቃውሞ ገጠመው

Date:



በፍሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የቀረበው የ60 በመቶ የክፍያ ጭማሪ በወላጆች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል። ትምህርት ቤቱ የላንቻ ቅርንጫፍ እንዳይዘጋ በሚል ሰበብ ጭማሪውን በግዴታ ለመጫን ሞክሯል በማለት ለካፒታል ቅሬታ ያቀረቡት ወላጆች፣ ሂደቱ ህጋዊ አሰራርን ያልተከተለና ስነ-ልቦናዊ ጫና የበዛበት ነው ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በተካሄደ ስብሰባ ላይ የሰሚት እና የሌሎች ቅርንጫፎች ወላጆች እንደገለጹት፣ በትምህርት ቤቱ የቀረበው አማራጭ “ወይ ጭማሪውን ተቀበሉ አለያም የላንቻ ቅርንጫፍ ይዘጋል” የሚል አስገዳጅ ይዘት ያለው ነው። ይህም በወላጆች ላይ የስነ-ልቦና ጫና በመፍጠር እና ህጋዊ አሰራርን ባልተከተለ መልኩ የተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

ምንም እንኳን ጭማሪው 60 በመቶ ቢባልም፣ “የክፍያ ማመጣጠኛ” በሚል በሚደረግ ማስተካከያ አጠቃላይ ክፍያው ለአንዳንድ ወላጆች ከ120 በመቶ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።

capital news

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ በቻይና ውይይት ያደርጋሉ 

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን መጪ ጉብኝት አስመልክቶ የክሬምሊን...

ከምዝገባ ካርድ ባሻገር፦ ለነገው ድምፅ የዛሬው ጥንቃቄ

ግዮን መጽሔት :- የምርጫ ካርድዎን በእጅዎ ይዘዋል? እንኳን ደስ...

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...