በፍሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የቀረበው የ60 በመቶ የክፍያ ጭማሪ በወላጆች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል። ትምህርት ቤቱ የላንቻ ቅርንጫፍ እንዳይዘጋ በሚል ሰበብ ጭማሪውን በግዴታ ለመጫን ሞክሯል በማለት ለካፒታል ቅሬታ ያቀረቡት ወላጆች፣ ሂደቱ ህጋዊ አሰራርን ያልተከተለና ስነ-ልቦናዊ ጫና የበዛበት ነው ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በተካሄደ ስብሰባ ላይ የሰሚት እና የሌሎች ቅርንጫፎች ወላጆች እንደገለጹት፣ በትምህርት ቤቱ የቀረበው አማራጭ “ወይ ጭማሪውን ተቀበሉ አለያም የላንቻ ቅርንጫፍ ይዘጋል” የሚል አስገዳጅ ይዘት ያለው ነው። ይህም በወላጆች ላይ የስነ-ልቦና ጫና በመፍጠር እና ህጋዊ አሰራርን ባልተከተለ መልኩ የተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን ጭማሪው 60 በመቶ ቢባልም፣ “የክፍያ ማመጣጠኛ” በሚል በሚደረግ ማስተካከያ አጠቃላይ ክፍያው ለአንዳንድ ወላጆች ከ120 በመቶ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።
capital news
በፍሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የ60 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ተቃውሞ ገጠመው
Date:
