አምስት ወደቦች ከባቡር ጋር

Date:


ኢትዮጵያ በዙሪያዋ ያሉ ወደቦችን በባቡር ለማገናኘት የ5 ሺህ ኪሎ ሜትር መስመር ጥናት ማጠናቀቋ ተሰማ

ኢትዮጵያ በርበራ፣ ሞምባሳ፣ ጂቡቲና ፖርት ሱዳንን ጨምሮ በዙሪያዋ ያሉ ሁሉንም ወደቦች በባቡር መስመር ለማገናኘት የ5 ሺህ ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር ጥናት ማጠናቀቋን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርዖ ሐሰን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በዙሪያዋ ያሉ ወደቦችን በባቡር ለማገናኘት ሰፊ ዕቅድ ይዛ እየሠራች ትገኛለች።

ጥናቱ የተጠናቀቀው የ5 ሺህ ኪሎ ሜትር መስመርም ይህንን የትስስር ዕቅድ ለማሳካት ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ባለሙያዎች ሥራውን ከተረከቡ በኋላ የጥገና አቅማቸውን እያሳደጉ መሆኑን የገለጹት አቶ በርዖ፤ ወደቦችን ለማገናኘት የተጠኑ አዳዲስ የባቡር መስመሮችም ወደ ተግባር እንዲገቡ አስፈላጊው ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምግባረ-መልካሙ ኢትዮጵያዊ

ስለሺ መንገሻ - ከ1934 እስከ 2018 ዓ.ም ሠሎሞን ለማ ገመቹ. ግዮን...

ትራምፕ ለኔታንያሁ ማስጠንቀቂያ ሰጡ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ...

ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ...

የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ከዓመታዊ የትርፍ 90 በመቶውን እንዲያከፋፍሉ ሊደረግ ነው

የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ተብለው የሚቋቋሙ ፈንዶች ከዓመት ትርፋቸው ቢያንስ...