ኢሎን መስክ ለኢራናውያን ኢንተርኔት በነጻ አቀረበ

Date:

የአሜሪካው ቢሊየነር ኢሎን መስክ ንብረት የሆነው የሳተላይት ኢንተርኔት አቅራቢ ስታርሊንክ፤ ለኢራናውያን ከክፍያ ነጻ የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት አቀረበ።

የኢራን መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ ያለውን የኢንተርኔት አቅርቦት በማቋረጡ ምክንያት በሳተላይት ለሚሠራው ለስታርሊንክ ወርሃዊ ክፍያ እየፈጸሙ ይጠቀሙ የነበሩ ኢራናውያን አገልግሎቱን በነጻ እንዲያገኙ መፍቀዱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ምንም እንኳን ስታርሊንክ በኢራን ውስጥ ሕገወጥ ቢሆንም፣ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ኢራናውያን በድብቅ አገልግሎቱን እንደሚጠቀሙ ዘገበው ጠቁሟል፡፡

የኢራን መንግሥት ከሚሰጠው የኢንተርኔት አገልግሎት ውጪ ቁጥጥር የሚያደርግበትን ስታርሊንክን ሲጠቀሙ የሚገኙ ሰዎች እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

ሦስት ሳምንት የሞላውን ተቃውሞ ተከትሎ፣ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ በመላው ኢራን ኢንተርኔት የተዘጋ ሲሆን፣ ባለሥልጣናትም ዜጎች ኢንተርኔት እንዳይጠቀሙ ለማገድ የስታርሊንክ ማገናኛ የሳተላይት ሳህኖችን እያሰሱ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...