ኬፕታውን እና ናይሮቢ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂን በመምራት ቀዳሚነቱን ይዘዋል።
ኬፕታውን በኮርፖሬት የ AI አጠቃቀም፣ በዳታ መሠረተ-ልማት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ ኢንቨስትመንት ረገድ ግንባር ቀደም ስትሆን፤ የአፍሪካዋ “ሲሊከን ሳቫና” በመባል የምትታወቀው ናይሮቢ ደግሞ በበለጸጉ የ AI ስታርታፕ ድርጅቶች፣ በዲጂታል ፈጠራና በቴክኖሎጂ ላይ በተመሰረቱ ፖሊሲዎቿ ጎልታ ትታያለች።
እነዚህ ሁለት ከተሞች ወጣት ተሰጥኦዎችን፣ ሥራ ፈጣሪነትንና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን መሠረት በማድረግ አፍሪካን በዓለም አቀፉ የ AI አብዮት ውስጥ እያደገች የመጣች ኃይል እንድትሆን በጋራ እያዘጋጇት ይገኛሉ።
