“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

Date:



አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር “የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል” በአዲስ አበባ ለመክፈት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል።

ይህ ማዕከል በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አካዳሚያዊ ትብብር፣ የባህል ልውውጥ እና የጋራ ምርምሮችን ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፤ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ማዕከሉ የዘመናትን የንግድና የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ውጤት ነው።

የቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ክቡር ዬ ሃይሊንግ፣ ማዕከሉ በቻይና መንግሥት ከሚደገፉ 25 ዓለም አቀፍ የምርምር ማዕከላት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ ስትራቴጂካዊ እርምጃ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ሁሉን አቀፍ አጋርነት ይበልጥ በማጠናከር፣ አዲስ የእውቀትና የልማት ምዕራፍ እንደሚከፍት ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ በቻይና ውይይት ያደርጋሉ 

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን መጪ ጉብኝት አስመልክቶ የክሬምሊን...

ከምዝገባ ካርድ ባሻገር፦ ለነገው ድምፅ የዛሬው ጥንቃቄ

ግዮን መጽሔት :- የምርጫ ካርድዎን በእጅዎ ይዘዋል? እንኳን ደስ...

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...