ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላት ዕጩ መልማይ ኮሚቴን ሰየሙ፡፡
ኮሚቴው በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 133/2011 አንቀጽ 5(1) መሠረት ነው ከመጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የተሰየመው፡፡
በዚህ መሰረትም፡-
- ቀሲስ ታጋይ ታደለ – ሰብሳቢ
- ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ – አባል
- አቶ ባዬ በዛብህ – አባል
- ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ – አባል
- አቶ ካሳሁን ፎሎ – አባል
- ወ/ሮ እርግበ ገ/ሐዋሪያት – አባል
- ወ/ሮ እንግዳዬ እሸቴ – አባል
- ሰብስብ አባፍራ አባጆብር – አባል
