የግብፅ የዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ ምክር ቤት በኤርትራ የካይሮ ዩኒቨርሲቲ ቅርንጫፍ እንዲቋቋም በይፋ አፅድቋል። ውሳኔው የግብፅ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዓለም አቀፋዊ ተደራሽነት ለማስፋት እና ከአፍሪካ አገራት ጋር ያለውን የትምህርት ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የተላለፈ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
የከፍተኛ ትምህርት እና ሳይንሳዊ ምርምር ሚኒስትሩ አብደልአዚዝ ኮንሶዋ በበላይነት በሩት ስብሰባ ላይ እንደገለጹት፣ የከፍተኛ ትምህርት አገልግሎትን ወደ ውጭ አገራት የመላክ ስትራቴጂያዊ ጥረቶች በተፋጠነ ሁኔታ መተግበር አለባቸው።
ይህ በኤርትራ የሚከፈተው አዲሱ ቅርንጫፍ በኤርትራና በአፍሪካ ቀንድ በትምህርት ዘርፍ ትልቅ አዎንታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል። ዕቅዱን በብቃት ለመከታተልም ከአካዳሚክ ባለሙያዎች የተዋቀረ ልዩ ኮሚቴ እንዲቋቋም መመሪያ ተሰጥቷል።
ምክር ቤቱ ከዚህ በተጨማሪ በመላው ግብፅ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የአስተዳደር አውቶሜሽንን ለማሳደግ ያለመ አጠቃላይ የኢንተርፕራይዝ ሀብት ዕቅድ ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ወስኗል። ይህንን አሰራር የሚቆጣጠር የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴም መዋቀሩ ተጠቁሟል።
