1 ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል መከበር ጀምሯል። በዓሉ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች እየተከበረ ነው፡፡
በበዓሉ አከባበር ሰላት እና ተክቢራን ጨምሮ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ተከናዉነዋልን ፡፡
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞቱን ገልጿል።
ህዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን አቅመ ደካሞችን በመደገፍ ኢስላማዊ እሴቱን ጠብቆ እንዲያከብርም ጥሪ አቅርቧል።
በዓሉ የነቢዩሏህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) ታማኝነት፣ መስዋዕትነትና ትዕግስት የሚታወስበት በመሆኑ ህዝበ ሙስሊሙ መንፈሳዊ እሴቱን ጠብቆ ሊያከብረው እንደሚገባ አስታውሷል።
በዓሉን በመረዳዳት እና በመተጋገዝ ማክበር እንደሚገባ ገልጾ፤ አቅመ ደካሞችን፣ ወላጆቻቸውን ያጡ ህጻናትንና ህሙማንን በመጠየቅና በመርዳት ማክበር ይገባል ብሏል።
