ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የ14 ሀገራት ኤምባሲዎች፤ በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት መግለጽ ላይ ያለው “ከፍተኛ ጫና” መቀጠሉ እንደሚያሳስባቸው ገለጹ። በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ተልዕኮ በበኩሉ የፕሬስ ነጻነት አለመኖር “መረጃ የማግኘት መብትን እና የመተቸት ነጻነትን ያጓድላል” ብሏል።
ኤምባሲዎቹ እና የአውሮፓ ህብረት ይህን ያሉት በዛሬው ዕለት በመላው ዓለም የሚከበረውን የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀን በማስመልከት በየፊናቸው ባወጡት መግለጫ ነው። ፈረንሳይ፣ ስዊድን፣ ኔዘርላንድስ፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና ኒውዚላንድ የተካተቱበት የ14 ሀገራት ስብስብ፤ በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ነጻ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ገለልተኛ ጋዜጠኝነት አስፈላጊነትን በመግለጫቸው አስታውሰዋል።
በመላው ዓለም ለሚገኙ ጋዜጠኞች ነጻነት እና ደህንነት መጠበቅ ያላቸውን ድጋፍ የገለጹት ሀገራቱ፤ በኢትዮጵያ አስተውለናዋል ያሉትን ወቅታዊ ሁኔታም አንስተዋል። በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት መግለጽ ላይ ያለው “ከፍተኛ ጫና” መቀጠሉን እንዳስተዋሉ የጠቀሱት ሀገራቱ፤ ይህ ሁኔታ እንደሚያሳስባቸውም በመግለጫቸው አስፍረዋል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15792/
@EthiopiaInsiderNews
#WorldPressFreedomDay