የሐማስ ታጣቂዎች ከእስራኤል ጋር በመተባበር የተከሰሱ ሰባት ሰዎችን ገደሉ

Date:

ሰኞ እለት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየተዘዋወረ ያለ ቪዲዮ እንደሚያሳየው የሐማስ ታጣቂዎች ከእስራኤል ጋር ተባብረዋል የተባሉ ሰባት ሰዎችን በጋዛ  እየጎተቱ ሲወስዷቸው ያሳያል።

ከዚያም እንዲንበረከኩ ከተደረጉ በኋላ ከኋላቸው በጥይት ተመተው ተገድለዋል። ቪዲዮው በሮይተርስ የተረጋገጠ ሲሆን ኤጀንሲው ስለ ትክክለኛነቱም ከሐማስ ምንጮች ማረጋገጫ አግኝቷል።

የዜና ምንጩ ግድያው ሰኞ ጥቅምት3 እንደተፈጸመም አረጋግጧል።

በርካታ ምስክሮች (እንዲሁም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚገኙ ቪዲዮዎች) የሰብዓዊ ዕርዳታ የሚጭኑ መንገዶችን ጨምሮ በጋዛ ውስጥ የታጠቁ የሐማስ ታጣቂዎችን ያሳያሉ።

የፍልስጤም የጸጥታ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ በቅርብ ቀናት በሐማስ ታጣቂዎች እና በተቀናቃኝ ቡድኖች መካከል በተፈጠረ ግጭት ውስጥ ደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...