ሰኞ እለት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየተዘዋወረ ያለ ቪዲዮ እንደሚያሳየው የሐማስ ታጣቂዎች ከእስራኤል ጋር ተባብረዋል የተባሉ ሰባት ሰዎችን በጋዛ እየጎተቱ ሲወስዷቸው ያሳያል።
ከዚያም እንዲንበረከኩ ከተደረጉ በኋላ ከኋላቸው በጥይት ተመተው ተገድለዋል። ቪዲዮው በሮይተርስ የተረጋገጠ ሲሆን ኤጀንሲው ስለ ትክክለኛነቱም ከሐማስ ምንጮች ማረጋገጫ አግኝቷል።
የዜና ምንጩ ግድያው ሰኞ ጥቅምት3 እንደተፈጸመም አረጋግጧል።
በርካታ ምስክሮች (እንዲሁም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚገኙ ቪዲዮዎች) የሰብዓዊ ዕርዳታ የሚጭኑ መንገዶችን ጨምሮ በጋዛ ውስጥ የታጠቁ የሐማስ ታጣቂዎችን ያሳያሉ።
የፍልስጤም የጸጥታ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ በቅርብ ቀናት በሐማስ ታጣቂዎች እና በተቀናቃኝ ቡድኖች መካከል በተፈጠረ ግጭት ውስጥ ደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል።
