ኦሮሚያ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቱን ለማስፋት እና የፋይናንስ አካታችነትን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት በመቀጠል በሁሉም የነዳጅ ማደያዎች የነዳጅ ግዢን በዲጂታል ክፍያ ለመፈፀም የሚያስችል “ሚልኪ” የተሰኘ አዲስ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ አድርጓል ።
ይህ መተግበሪያ ለነዳጅ ማደያ ሰራተኞች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከማስቀረት ባለፈ በማደያዎቹ የሚቀመጥ የገንዘብ መጠን እንዲቀንስ በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚቀንስ ይጠበቃል።
ኦሮሚያ ባንክ ከአዲሱ መተግበሪያ በተጨማሪ ከነዳጅ ማደያ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ የተለያዩ አዳዲስ የባንክ አገልግሎቶችን ይዞ መምጣቱን ገልጿል።
Source: capitalethiopia
