በፍሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የ60 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ተቃውሞ ገጠመው

Date:



በፍሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የቀረበው የ60 በመቶ የክፍያ ጭማሪ በወላጆች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል። ትምህርት ቤቱ የላንቻ ቅርንጫፍ እንዳይዘጋ በሚል ሰበብ ጭማሪውን በግዴታ ለመጫን ሞክሯል በማለት ለካፒታል ቅሬታ ያቀረቡት ወላጆች፣ ሂደቱ ህጋዊ አሰራርን ያልተከተለና ስነ-ልቦናዊ ጫና የበዛበት ነው ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በተካሄደ ስብሰባ ላይ የሰሚት እና የሌሎች ቅርንጫፎች ወላጆች እንደገለጹት፣ በትምህርት ቤቱ የቀረበው አማራጭ “ወይ ጭማሪውን ተቀበሉ አለያም የላንቻ ቅርንጫፍ ይዘጋል” የሚል አስገዳጅ ይዘት ያለው ነው። ይህም በወላጆች ላይ የስነ-ልቦና ጫና በመፍጠር እና ህጋዊ አሰራርን ባልተከተለ መልኩ የተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

ምንም እንኳን ጭማሪው 60 በመቶ ቢባልም፣ “የክፍያ ማመጣጠኛ” በሚል በሚደረግ ማስተካከያ አጠቃላይ ክፍያው ለአንዳንድ ወላጆች ከ120 በመቶ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።

capital news

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝች

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ጽጋብ እና ሽቶ...

“አዳም አንድ ደራሲ የሚያስፈልጉት ሁሉም ግብዓቶች ተሟልተው ያሉት ፀሐፊ ነው”

አዳም ረታ ሥራዎቹን ለአንባቢ ማድረስ የጀመረው ከ1970ዎቹ አንስቶ ነው።...

ከፍተኛ የግብር ክፍያ በሕጋዊ ነጋዴው ላይ በመጫን ሲፈጽሙት …

መንግስት ከግብር የሚያገኘው ገቢ የቀነሰው ወይም ከሀገር ውስጥ አጠቃላይ...

ሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም እውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብር ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

የአዲስ አበባ ሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማኅበር ሁለተኛውን የሆስፒታሊቲ...