ከኡጋንዳ ወደ ኢትዮጵያ የመጀመሪያው በፋብሪካ የተቀነባበረ  የበሬ ሥጋ ንግድ ተጀመረ

Date:

‘ራንቸርስ ፋይነስት’ የተባለው የኡጋንዳ የግል ሥጋ አቀናባሪ ኩባንያ፣ በየወሩ 20 ቶን የስቴክ፣ የቋሊማና የበግ ሥጋ ምርቶችን ለኢትዮጵያው ‘ዳይመንድ ሆቴልና ሬስቶራንት ግሩፕ’ ለማቅረብ ስምምነት ተፈራርሟል።

​የኡጋንዳ ባለሥልጣናት ይህንን ስምምነት ለአገሪቱ የእንስሳት ዘርፍ ትልቅ እቅስቃሴና እሴት በመጨመር ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የተደረገ ስኬት ነው ብለውታል።

ጥሬ ሥጋን በኪሎ 4 ዶላር ከመሸጥ ይልቅ በማቀናበር እሴት ጨምሮ እስከ 50 ዶላር መሸጥ እንደሚቻልም ጠቅሰዋል።

​ኢትዮጵያ የተመረቱ የምግብ ምርቶች ገበያን እያሰፋች ሲሆን፣ በቅርቡ ከብራዚልና ከአሜሪካም መሰል የእንስሳትና የግብርና ምርቶችን ለማስገባት ፈቃድ መስጠቷ ይታወሳል።

ምንጭ:  ኡጋንዳ ናየል ፖስት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ 50 ሚሊዮን የሚገመቱ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ እንደማያገኙ ተነገረ

በኢትዮጵያ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን በበቂ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችል...

ገዳ ባንክ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፍኩ አለ

ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ113 በመቶ እድገት አሳይቷል ...

እስራኤል የኢራን ተደራዳሪዎችን ለመግደል እያሴረች እንደነበር ተዘገበ

አሜሪካና ኢራን ወሳኝ የሆነውን የተኩስ አቁም ስምምነት በደረሱበት እስራኤል...

ክፍያ በመቀበል የባንክ ሂሳብ ቁጥራቸውን የሚያከራዩ በዝተዋል

የባንክ ሂሳብ ቁጥርን በመሸጥና በማከራየት የሚፈጸም የማጭበርበር ወንጀል መበራከቱን...