የጋምቤላ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጁሉ ጊሎ እንደፈለጹት ባለፉት ዘጠኝ ወራት አንድ ሺህ 850 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማስገባት ታቅዶ፤ 4ሺህ 254 ኪሎ ግራም ወርቅ ገቢ ማድረግ ተችሏል፡፡
እንደ ኢፕድ ዘገባ በክልሉ በአብዛኛው ወርቅ በባሕላዊ መንገድ በልዩ አነስተኛ ማህበራት እንደሚመረት ሲሆን ወርቅ ለማምረት ፍቃድ ወስደው በሕጋዊ መንገድ ወርቅ እያመረቱ ያሉ እንዳሉ ሁሉ፤ ፍቃድ ሳይኖራቸው በተለምዶ ወደ ወርቅ ማምረት ሥራ ገብተው እየሠሩ ያሉ መኖራቸውም ተገልጿል ፡፡
በክልሉ ከፍተኛ የወርቅ ክምችት አለባቸው ተብለው የተለዩት ወረዳዎች ጋምቤላ ፣ አቦቦ፣ መንገሺና ዲማ ናቸው ፡፡
