የሰላም ስምምነቱ 90 በመቶ ዝግጁ ነው – ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ

Date:

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ሀገራቸው ከሩሲያ ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለመቋጨት የሰላም ስምምነቱ 90 በመቶ ዝግጁ ነው አሉ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት የፈረንጆቹን 2026 አዲስ ዓመት አስመልከቶ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእከት ነው፡፡

ዜሌንስኪ በመልእክታቸው፤ ለአራት ዓመታት ገደማ የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት ድርድር 10 በመቶ ብቻ ይቀረዋል ብለዋል፡፡

የሰላም ስምምነቱ የቀጠናውን ሰላም ብሎም የዩክሬንን እና የአውሮፓን እጣ ፈንታ የሚወስን ነው ሲሉም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።

ዩክሬን ሰላምን ለማስፈን ስትል ሁሉንም ማጣት ባትሻም ለሀገሪቱ ህልውና መቀጠል ጦርነቱን መቋጨት ያስፈልጋል ብለዋል።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በበኩላቸው፤ የሩሲያን የማይበጠስ አንድነት፣ የጋራ መደጋገፍ እና የመጪ ግዜ ብሩህ ተስፋ አጠናክረን እንቀጥል ሲሉ ለህዝባቸው ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእከት ገልጸዋል።

የሩሲያን ጀግና ወታደሮች እናመሰግናለን ያሉት ፕሬዝዳንት ፑቲን፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሩሲያውያን በመንፈስ ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪ ማቅረባቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...