“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

Date:



አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር “የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል” በአዲስ አበባ ለመክፈት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል።

ይህ ማዕከል በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አካዳሚያዊ ትብብር፣ የባህል ልውውጥ እና የጋራ ምርምሮችን ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፤ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ማዕከሉ የዘመናትን የንግድና የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ውጤት ነው።

የቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ክቡር ዬ ሃይሊንግ፣ ማዕከሉ በቻይና መንግሥት ከሚደገፉ 25 ዓለም አቀፍ የምርምር ማዕከላት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ ስትራቴጂካዊ እርምጃ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ሁሉን አቀፍ አጋርነት ይበልጥ በማጠናከር፣ አዲስ የእውቀትና የልማት ምዕራፍ እንደሚከፍት ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝች

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ጽጋብ እና ሽቶ...

“አዳም አንድ ደራሲ የሚያስፈልጉት ሁሉም ግብዓቶች ተሟልተው ያሉት ፀሐፊ ነው”

አዳም ረታ ሥራዎቹን ለአንባቢ ማድረስ የጀመረው ከ1970ዎቹ አንስቶ ነው።...

ከፍተኛ የግብር ክፍያ በሕጋዊ ነጋዴው ላይ በመጫን ሲፈጽሙት …

መንግስት ከግብር የሚያገኘው ገቢ የቀነሰው ወይም ከሀገር ውስጥ አጠቃላይ...

ሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም እውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብር ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

የአዲስ አበባ ሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማኅበር ሁለተኛውን የሆስፒታሊቲ...