የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከVISA ጋር በመሆን በሰሜን አሜሪካ በሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ላይ በተመልካችነት ለመሳተፍ የሚያስችል ዕጣ የሚያስገኘውን “ጉዞ ወደ ፊፋ የዓለም ዋንጫ 2026” ዘመቻ በይፋ አስጀምሯል።
ዕጣው በካርዱ ግብይት ለሚፈጽሙ የኮፕ VISA ካርድ ደንበኞች የዕጩነት የዕጣ ቁጥር በማደል ዕድለኛ ለሚሆኑ ሁለት፥ ደንበኞች እያንዳንዳቸው በአንድ ተጨማሪ ሰው ታጅበው ቪዛ፣ የደርሶ መልስ የአየር ትኬት፣ ሆቴልና ምግብ፣ የጨዋታ ትኬቶችና ተዛማጅ ወጪዎችን ያካተተ ሙሉ ፓኬጅ ያስገኛል ተብሏል።
በዕጣው ብቁ የሚያደርጉ ግብይቶችም፥ በቪዛ ክላሲክ ዴቢት ካርዶች የተከናወኑ የሀገር ውስጥ ፖስ እና የኢ-ኮሜርስ ክፍያዎች(በመደበኛና በኮፕባንክ አልሁዳ) የሚከናወኑ ግብይቶች፣ በቪዛ ክላሲክ ፕሪ ፔይድ ካርዶች የሚፈጸሙ ዓለም አቀፍና ኦንላይን ክፍያዎች፣ በቪዛ ፕላቲኒየም ፕሪ ፔይድ ካርዶች የሚከናወኑ ፕሪሚየም ዓለም አቀፍ ግብይቶችና በሁሉም ምድቦች የሚከናወኑ ‘ኮንታክትለስ’ ክፍያዎች መሆናቸውንም አስታውቋል።
