የአሜሪካ ኮንግረስ ለሶማሊላንድ ታሪካዊ ረቂቅ ሕግ አዘጋጀ

Date:

የአሜሪካ ሕግ አውጪዎች ሶማሊላንድ ለዓመታት የቆየባትን የፋይናንስ ማግለል በመስበር በቀጥታ ከዓለም አቀፉ ኢኮኖሚ ጋር እንድትገናኝ የሚያስችል አዲስ ረቂቅ ሕግ ለኮንግረሱ አቅርበዋል።

ይህ እርምጃ ዋሽንግተን ለአፍሪካ ቀንድ ያላትን የጂኦፖለቲካዊ ፖሊሲ የቀየረ ትልቅ ክስተት ተደርጎ የተወሰደ ሲሆን፣ ረቂቅ ሕጉ ከ6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆነው የሶማሊላንድ ሕዝብ የSWIFT የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን ጨምሮ ሀገሪቱ ከዓለም አቀፍ የባንክ መሠረተ ልማት ጋር እንድትተሳሰር የሚያስችሉ ግልጽ የሆኑ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል።

በተጨማሪም የአሜሪካ የግምጃ ቤት ሚኒስቴር በ180 ቀናት ውስጥ ኃላፊነት የተሞላበት የአሜሪካ ኢንቨስትመንት በሶማሊላንድ የሚስፋፋበትን ስትራቴጂ እንዲያዘጋጅ የሚያዝዝ ሲሆን፣ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እና በሽብርተኝነት ላይ የሚደረገውን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

ረቂቅ ሕጉ ከጸደቀ ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መከፈት፣ የንግድ መስመሮች መስፋፋት እና ሶማሊላንድ በቀጣናው ቁልፍ የኢኮኖሚ መተላለፊያ ሆና እንድትወጣ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...