“የሟችም የገዳይም እናት እኔ ነኝ”

Date:

​”የሟችም የገዳይም እናት እኔ ነኝ” በሚል መሪ ሀሳብ በኢትዮጵያ የእምነት እናቶች ሀገራዊ ፈዉስና ሰላምን ለማምጣት የ3 ቀናት ብሔራዊ የንስሀ ጥሪ አስተላለፉ።

​እናቶቹ ሀገሪቱ በአሁን ወቅት ካለችበት ማህበራዊ፣ ሥነ-ምግባራዊ እና ሰብአዊ ቀውስ ወጥታ ዘላቂ ሰላም እንድታገኝ ለአባቶች እና ለሃይማኖት ተቋማት መሪዎች የሰላም ጥሪ አቅርበዋል።

በመፈናቀል፣ በሙስና መስፋፋትና በግጭቶች ምክንያት የሚደርሰውን ስቃይ በጋራ እየተጋሩ መሆኑን የገለጹት እናቶቹ፤ “የሟችም የገዳይም እናት እኔው ነኝ” በሚል የእናትነት መንፈስ የችግሩ ሰለባ የሆኑትን ሁሉ ማስታገስና ማዳን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

​በአሁኑ ወቅት ሰብአዊ ማንነት ተንቆ፣ ቋንቋን ጣዖት በማድረግ የሚሰራጩ የጥላቻ ትርክቶች፣ ቂም በቀል እና የእርስ በእርስ ግጭቶች ሀገርንና ትውልድን እያደሙ እንደሚገኙም በምሬት ገልጸዋል።

ይህን ተከትሎም ሁሉም ኢትዮጵያውያን በተመሳሳይ ቀናት ወደ ፈጣሪ የሚጮኹበትና ይቅርታ የሚጠይቁበት ብሔራዊ የ3 ቀናት የጾምና ጸሎት (የንስሐ አዋጅ) በጋራ እንዲታወጅ እናቶች አሳስበዋል።

​የሃይማኖት አባቶች ሀገርን ከጥፋት የመጠበቅና ትዉልድን የማዳን ሀገራዊ መለከት እንዲያወጁም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

​#የሟችምየገዳይምእናትእኔነኝ #የእናትነትመንፈስ #የሰላምጥሪ #ሀገራዊፈውስ #የንስሐአዋጅ #ሰላምለኢትዮጵያ #የእምነትእናቶች #ኢትዮጵያ #PeaceForEthiopia #MothersForPeace #Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...