ቼልሲ የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ

Date:

ቼልሲ ሪያል ቤቲስን 4 ለ 1 በማሸነፍ የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል።

ዛሬ ምሽት በተደረገው የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ሪያል ቤቲሶች 1 ለ 0 እየመሩ ዕረፍት መውጣት ቢችሉም ቼልሲዎች ከዕረፍት መልስ ባስቆጠሯቸው 4 ግቦች ሻምፒዮናነቱን ተጎናፅፈዋል። 

ሪያል ቤቲስን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ ኤዛልዙሊ በ9 ደቂቃ ቢያስቆጥርም ቼልሲን አሸናፊ ያደረጉ ግቦችን ኢንዞ ፌርናንዴዝ፣ ጃክሰን 70ኛ፣ ጄደን ሳንቾ በ83ኛ እና ካይሴዶ በ91ኛ ደቃቂዎች ላይ አስቆጥረዋል።

የእንግሊዙ ክለብ ቼልሲ ዛሬ ምሽት የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግን ማሸነፉን ተከትሎ አራቱንም የአውሮፓ እግርኳስ ማኅበር የሚያዘጋጃቸው የክለብ ውድድሮች ያሸነፈ የመጀመሪያው ክለብ ሆኗል።

ሰማያዊዎቹ ከዚህ በፊት ዩኤፋ የሚያዘጋጃቸውን ሦስቱን ውድድሮች ማለትም ሻምፒየንስ ሊግ፣ ዩሮፓ ሊግ እና የሱፐር ካፕ አሸናፊዎች ዋንጫዎችን ማሸነፋቸው ይታወሳል።

ዛሬ ምሽት የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ዋንጫን በማሸነፋቸው አራቱንም የዩኤፋ ታላላቅ የክለብ ውድድሮች ዋንጫ ያሸነፈ የመጀመሪያው ክለብ ሆኗል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...