‘ራንቸርስ ፋይነስት’ የተባለው የኡጋንዳ የግል ሥጋ አቀናባሪ ኩባንያ፣ በየወሩ 20 ቶን የስቴክ፣ የቋሊማና የበግ ሥጋ ምርቶችን ለኢትዮጵያው ‘ዳይመንድ ሆቴልና ሬስቶራንት ግሩፕ’ ለማቅረብ ስምምነት ተፈራርሟል።
የኡጋንዳ ባለሥልጣናት ይህንን ስምምነት ለአገሪቱ የእንስሳት ዘርፍ ትልቅ እቅስቃሴና እሴት በመጨመር ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የተደረገ ስኬት ነው ብለውታል።
ጥሬ ሥጋን በኪሎ 4 ዶላር ከመሸጥ ይልቅ በማቀናበር እሴት ጨምሮ እስከ 50 ዶላር መሸጥ እንደሚቻልም ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ የተመረቱ የምግብ ምርቶች ገበያን እያሰፋች ሲሆን፣ በቅርቡ ከብራዚልና ከአሜሪካም መሰል የእንስሳትና የግብርና ምርቶችን ለማስገባት ፈቃድ መስጠቷ ይታወሳል።
ምንጭ: ኡጋንዳ ናየል ፖስት
