ከውጪ ዕርዳታ ቁርጥራጮች የምንጠብቅበት ጊዜ አይደለም

Date:

የአፍሪካ መሪዎች በዚህ ሳምንት በአቢጃን እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ልማት ባንክ ቡድን የ2025 ዓመታዊ ስብሰባዎች ላይ አህጉሪቱ የራሷን ካፒታል እንድታንቀሳቅስ እና የክልላዊ ውህደትን እንድታፋጥን ጠንካራ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ ጥሪ የቀረበው፣ 47 የአፍሪካ አገራትን የሚነኩ አዳዲስ የአሜሪካ ታሪፎችን ጨምሮ በሚለዋወጠው ዓለም አቀፍ የንግድ ሁኔታዎች ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።

በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ የአሥር ዓመቱን የሥራ ዘመናቸውን የሚያጠናቅቁት የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንዉሚ አዴሲና፣ ባደረጉት የስንብት ንግግር፣ “ይህ ከውጭ ዕርዳታ ቁርጥራጮች የምንጠብቅበት ጊዜ አይደለም” በማለት ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

አዴሲና አክለውም፣ “አፍሪካ የራሷን ሀብት – ሰብዓዊ፣ ፋይናንስ፣ ተፈጥሮአዊ – መክፈትና ሁሉን አቀፍ ዕድገትን የሚያበረታቱ ውስጣዊ የእሴት ሰንሰለቶችን መገንባት አለባት” ሲሉ አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...