የስፔስኤክስ የህዋ ጉዞ ሙከራ ለምን ከሸፈ?

Date:



የኢሎ
ን መስክ የሕዋ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው ስፔስኤክስ የሰውን ልጅ ወደማርስ የመውሰድ ምርምር አካል የሆነች “ስታርሺፕ” ሮኬት ለሙከራ ቢያመጥቅም፣ ከ30 ደቂቃ የአየር ላይ ቆይታ በኋላ መበታተኗ ታውቋል።

በስፔስኤክስ የሰውአልባ ሮኬት ላይ ተመሳሳይ አደጋ ሲያጋጥም የአሁኑ ለሦስተኛ ጊዜ ነው።

ከአሜሪካ ቴክሳስ የሕዋ ማምጠቂያ ጣቢያ  እንድትወነጨፍ ቢደረግም በነዳጅ ማከማቻዋ ላይ ያጋጠመው ፍሳሽ ለአደጋው ምክንያት መሆኑን ስፔስ ኤክስ አስታውቋል። 

ስፔስኤክስ በሰጠው መግለጫ “ስታርሺፕ ቅፅበታዊና ያልተጠበቀ የመበታተን አደጋ አጋጥሟታል፤ መረጃዎችን በመገምገም ለቀጣዩ ሙከራ የምናደርገው ጥረት ይቀጥላል” ሲል ሁኔታውን አስረድቷል።

የአሜሪካን የፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር በበኩሉ በሰጠው መግለጫ “በስፔስኤክስ ስታርሺፕ 9 ተልዕኮ ወቅት ችግር መከሰቱን አረጋግጦ፤ በሮኬቷ ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ በሰውም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...