ሊቨርፑል ጄረሚ ፍሪምፖርግን ከባየር ሊቨርኩሰን አስፈረመ

Date:

ሊቨርፑል የባየር ሊቨርኩሰኑን የቀኝ መስመር ተከላካይ ጄረሚ ፍሪምፖንግን በ30 ሚሊዮን ዮሮ የዝውውር ሂሳብ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል ። 

በስምምነቱ መሠረት ፍሪምፖንግ በሊቨርፑል ቤት ለ5 ዓመታት የሚቆይ ይሆናል።

ሊቨርፑል የአንፊልዱ ኮከብ ትሬንት አሌክሳንደር ወደ ማድሪድ መቀላቀሉን ይፋ ካደረገ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ኔዘርላንዳዊውን ኢንተርናሽናል ተጫዋች ማስፈረሙን  አረጋግጧል።

ሁለገቡ የቀኝ እግር ተጫዋች ፍሪምፖንግ በአርኔ ስሎት ቡድን ውስጥ የአሌክሳንደር አርኖልድ ምትክ ሆነው ይጫወታሉ ተብለው ከሚጠበቁ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሆኗል።

በልጅነቱ በማንቸስተር ሲቲ ቤት ሰልጥኖ ያደገው ሆላንዳዊው በ2021 ወደ ሊቨርኩሰን ከመዛወሩ በፊት በ2019 ለሴልቲክ ተጫውቷል።

ፍሪምፖንግ በሊቨርፑል ቤት የሀገሩ ኮከቦች ከሆኑት ቨርጂል ቫን ዲጅክ፣ ኮዲ ጋክፖ እና ራያን ግራቨንበርች ጋር ተቀላቅሏል።

ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...

በፌደራሉ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተገለጸ

ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ በሚገኝ...

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...