በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ከአሜሪካ ጦር ሃይል ከፍተኛ አዛዦች ዘንድ የተሰማው ምስጢራዊ ማስጠንቀቂያ መላውን አለም አነጋግሯል።
የአሜሪካ አውሮፓ እዝ አዛዥ ጄኔራል አሌክሰስ ግሪንኬቪች ለፔንታጎን በላኩት አስቸኳይ ደብዳቤ፣ በአካባቢው ያለው የጦር መርከቦች እጥረት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ይፋ አድርገዋል።
ጄኔራሉ ባስተላለፉት የላቀ ማስጠንቀቂያ፣ በአስቸኳይ ተጨማሪ አጥፊ የጦር መርከብ ካልተመደበላቸው፣ እስራኤልን ከኢራን ሚሳኤሎች ከመከላከል ይልቅ የአሜሪካን ግዛት ደህንነት ለማስቀደም ሊገደዱ እንደሚችሉ አስታውቀዋል።
ወራት በተሻገረው ተደጋጋሚ ውጊያ ምክንያት የአሜሪካ የጦር መርከቦች ከፍተኛ የቴክኒክ ጥገና እየፈለጉ ሲሆን፣ የሚሳኤል መከላከያ ክምችታቸውም በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተጠቅሷል።
በአንድ በኩል የሩሲያን አቪዬሽንና ሚሳኤል ስጋት የመጠበቅ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የእስራኤልን ሰማይ ከኢራንና ሁቲዎች ጥቃት የመታደግ ሁለት ግዙፍ ተልእኮዎች በአንድ ጊዜ የተደቀኑበት የአሜሪካ ጦር ሃይል፣ አሁን ላይ ከባድ የሃብትና የጦር መሳሪያ እጥረት እንደገጠመው የፔንታጎን ምንጮች አረጋግጠዋል።
