“ሰላም በብዝኅ ሃይማኖት ማኅበረሰብ” የተሰኘ መጽሐፍ ተመረቀ

Date:

በሊቀ ትጉሀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የተሰናዳ “ሰላም በብዝኅ ሃይማኖት ማኅበረሰብ” የተሰኘ መጽሐፍ ዛሬ ቅዳሜ ሚያዚያ 4 2017 ዓ.ም ተመርቋል።


በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ የቦርድ ሰብሳቢ ; ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደብባዊ ዞን ማይጨው ሀገረ ስብከት ; እና በመንበረ ፓትርያርክ የቅርስ ጥበቃና ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር እና የማኅበራት ማደራጃ፣ ምዝገባና ቁጥጥር መምሪያ ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ የሰላም ሚኒስትር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኸይረዲን ተዘራ ; የቤተእምነት መሪዎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ
ዶ/ር ኸይረዲን ተዘራ እንደገለጹት የሰላም ጉዳይ የሁሉም ጉዳይ እንደመሆኑ የእያንዳንዱ ሰው አስተዋፆ ለሰላም ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው መጽሐፉ ጸሐፊው ለሰላም በሚደረገው ሂደት ላላቸው አስተዋፆ ገጸ በረከት እንደሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ በበኩላቸው መጽሐፉ ለሀገራዊ ምክክሩ ግብዓት ሆኖ እንደሚያገለግል ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ የኪነጥበብ ሰዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...

ኢራን ድርድር ውስጥ ከገባች “እጇ ከቃታው ላይ” አይነሳም

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ድርድር የምታደርግ ከሆነ ንግግር ውስጥ የምትገባው...

ለቅርስ ጥበቃና ምርምር የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም

የቅርስ ጥበቃና የምርምር ዘርፍ ውስጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስፈላጊ...